www.maledatimes.com የአውሮፕላን ጠለፋውና የህወሃት አመራሮች ስብሰባ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የአውሮፕላን ጠለፋውና የህወሃት አመራሮች ስብሰባ

By   /   February 18, 2014  /   Comments Off on የአውሮፕላን ጠለፋውና የህወሃት አመራሮች ስብሰባ

    Print       Email
0 0
Read Time:7 Minute, 46 Second

ከወሰንሰገድ ገ/ኪዳን 

የኢህአዴግ አመራሮች ለአስቸኳይ ጉዳይ ቤተመንግስት ተጠርተዋል:: ሊቀመንበሩን የስብሰባውን አጀንዳ መናገር ጀመሩ::

እንደምታውቁት መጪው 2007 የምርጫ ጊዜ ነው:: እና ጠላቶቻችን ከአሁኑ ምርጫው ; ፓርቲው እና አገሪትዋ ላይ አደጋ ለማድረስ እየሞከሩ ነው:: ለዛ ምሳሌ የሚሆነው እና ዛሬ የተሰበብንበት ምክንያት ትላንት የተጨናገፈው የአውሮፕላን ጠለፋ ነው:: ፓርቲያችን እንደ ትላንት አይነቱ ጸረ-ልማት የሆነ ተመሳሳይ ተግባር እንዳይፈጸም ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት:: ለዚህም አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይጠበቅብናል::
በእዚህ አጀንዳ ላይ ያላችሁን አስተያየት ስጡና እንወያይበት::

አንዱ አመራር እጁን አወጣ:: እንዲናገርም ተፈቀደለት::

<<ሁሉም የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ጋር ፌዴራል ፖሊስ መመደብ አለበት:: ለሚኒባስ ታክሲ አንድ ;ለአውቶቡስ ሁለት ከፊት እና ከኋላ ይመደብ:: ምንም እንኳን ኢኮኖሚ ው የሚጎዳ ቢሆንም መጪው ምርጫ ላይ ፈጽሞ አደጋ እንዲጋለጥ መፍቀድ የለብንም::>>
እሱ ተናግሮ እንዳበቃ ሌላኛው እጁን አወጣ::

<<ይሄ የጠለፋ ተግባር ጥልቅ ምርመራ ያስፈልገዋል:: የጠለፋ ወንጀል ጉዳቱ የከፋ ነው:: ለዚህ አደገኛ የአሽባሪዎች ስራ ሊጋለጡ የሚችሉ የህብረተስብ አካላቶችን ለይተን ማውጣት አለብን:: ከዚህ ቀደም በሌላ የጠለፋ ወንጀል እንዲሁም ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን ፖሊስ የቅርብ ክትትል ሊያደርግባቸው ይገባል:: ሴት የጠለፉ ; ሊጠልፉ ሲሉ የተያዙ ; ወይም የሴት ጠለፋቸው የከሸፈባቸው ሰዎች ፖሊስ የትኩረቱ አካላት ያድርጋቸው:: ጠለፋ እንደሌሎች ወንጀሎች ተዛማጅ ነው:: ከዚህም አንጻር የሀገር ቀሚስ ጠለፋ ላይ የተሰማሩ ሰዎች ለሴት ጠለፋ ወንጀል የተጋለጡ እንደሆነ ከዚህ በፊት የተደረገ ጥናት ያሳያል:: ስለዚህም ፖሊስ ጨርቆስ እና ሽሮሜዳ አካባቢ ያሉ ጥልፍ እና ቀሚስ ጠላፊዎችን ትኩረት ቢያደርግባቸው ክፋት ያለበት አይመስለኝም:: ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ እንዲሉ ለጠለፋ የሚያጋልጡ ቀዳዳዎች ን ሁሉ መድፈን አለብን::>>

ሌላኛው ቀጠለ

<<ፓርላማው አሸባሪ ተብሎ ከፈረጃቸው ከእነ ግንቦት ሰባት እና አል-ሸባብ በተጨማሪ ጠላፊዎችን መጨመር ይጠበቅበታል:: ለዚህም ህግ አርቃቂው ኮሚቴ ህጉን እንዲያሻሽል ይደረግ::>>
ሌላኛው አከለ

<<ለጥንቃቄ ያህል ከእንግዲህ አይሮፕላኖቻችንን ማብረር ያለባቸው የፓርቲ አባላቶች ብቻ መሆን አለባቸው::በተለይ ከፍተኛ ባለስልጣኖች የሚጓዙበት አይሮፕላኖች በታማኝ አባሎቻችን መሆን አለባቸው:: አባል ያልሆኑ ፓይለቶች ሆኑ ኮፓይለቶች እንዲሁም ሆስተሶች አባል የሚሆኑበት መንገድ ይመቻች:: አድር ባይ እና ኪራይ ሰብሳቢ ያልሆኑ ሀቀኛ የአይሮፕላን ሰራተኞች ማፍራት ይጠበቅብናል:: አባል መሆን የማይፈልጉ ወይም ተቃዋሚ ፓርቲን የመደገፍ ዝንባሌ የሚያሳዩ ሰራተኞች ከስራቸው መሰናበት አለባቸው:: በምትኩም ታማኝ እና አንጋፋ አባሎቻችን የማብረር ትምህርቱ ተሰጥቷቸው ስራውን እንዲቀላቀሉ ይደረግ::>>

ሌላኛው የህወሃት አመራር እንዲህ አለ

<<ይሔ ጠለፋ የተካሄደው በጠላቶቻችን የተቀነባበረ ሴራ ነው:: ለካቲት 11ን የትግራይ ህዝብ እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በደስታ እንዳያከብር ለማድረግ ሆን ተብሎ የታሰበ ስለሆነ የህውሃት አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም የብአዴን ; ኦህዴድ እና ድህአዴግ እንዲሁም አጋር ፓርቲዎች ጠለፋውን የሚያወግዝ ሰልፍ ህዝቡ እንዲወጣ የተለመደውን ቅስቀሳ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል::>> አለ

በስብሰባው መጨረሻ ፓርቲው ጠለፋውን የሚያወግዝ ጽሁፍ አውጥቶ እና ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ላይ በመወሰን አምራሩ ተበተነ::
በነጋታውም በከተማው የታክሲ እና አውቶቡስ ተሳፋሪ መጫኛ እና ማውረጃ ቦታዎች ላይ የፌዴራል ፖሊሶች ተመድበው ተሳፋሪው ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገበት መሳፈር እና መውረድ ጀመረ::

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on February 18, 2014
  • By:
  • Last Modified: February 18, 2014 @ 10:08 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar