www.maledatimes.com የማለዳ ወግ … እነሆ የጨለመው ነጋ ! … ነጻ ወጣሁ ! አመሰግናለሁ (ጋዜጣኛ ነብዪ ሲራክ) - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የማለዳ ወግ … እነሆ የጨለመው ነጋ ! … ነጻ ወጣሁ ! አመሰግናለሁ (ጋዜጣኛ ነብዪ ሲራክ)

By   /   May 3, 2014  /   Comments Off on የማለዳ ወግ … እነሆ የጨለመው ነጋ ! … ነጻ ወጣሁ ! አመሰግናለሁ (ጋዜጣኛ ነብዪ ሲራክ)

    Print       Email
0 0
Read Time:5 Minute, 31 Second

እነሆ 60 ፈታኝ የመከራ ቀናቶች በትዕግስት ተገፍተው አለፉ ፣ ክፉውን ቀን ለማለፍ የትዕግስት ጽናት ብርታት ተስፋየ ምንጩ
በመላ አለም የምትገኙ ወገን ወዳጆቸ ነበራችሁና ላደረጋችሁልኝ እና ላሳያችሁልኝ የሞራል ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቀርባለሁ !
አሰልችውን ቢሮክራሲ አልፈው ፣ በማይጨበጠው ቀጠሮ ሳይሰላቹ ሌት ተቀን እኔን ሀፐነው ታመው ጉዳዬን ለምስለኔ አቅርበው
ድቅድቅ ጨለማው እነወዲገፈፍልኝ ያደረጉትን ለማመስገን ቃላት ያጥረኛል ! ለደህንነታቸው ስል በስም ለማንሳት የማይቻለኝ
ወንድሞቸ ብርታት ፈጣሪ ታክሎበት ለዛሬው ንጋት ደርሻለሁ ! ተመስገን ! ነግቶም በአይኔ ሲንቀዋለሉ ከነበሩት ብላቴና ልጆቸና
ከመላ ቤተስብ ዘመደ አዝማድ ጓደኛ አፍቃሪዎቸ ለመገናኘቴ ምክንያት እናነተ በአካል ከጎኔ የቆማችሁ ነበራችሁና በሁሉም ስም
ምስጋና ወደር የለውም !
ከማዕከላዊው የብሪማን እስር ቤት ወዳጆቸ …በብሪማን ያላፉ ኢትዮጵያውያን
የህግ ታሳሪዎች መካከል በግፍ የታሰሩት አሰገራሚ ታሪኮችን ከእናንተው ጋር
በአካል ተገኝቸ ” እህ ” ሰምቸ ተምሬባቸዋለሁ ። በእስር ቤቱ ታዛ እና ግድግዳዎች
ላይ የጻፏቸው ማስታወሻና ጥቅሶችን ተመልክቸ ተጽናንቸባቸዋለሁ ። አንዷ
ተደጋግማ የሰማኋት ጥቅስ ውስጥ እኔም በመከራው ሳልፍ ተስፋን ሰንቄ እዚህ
ደርሻለሁ! ” እኔ መውጣት የምፈራው መውጣት ከማልችለው ከመቃብር እንጅ ፣
መውጣት ከምችለው የብሪማን ወህኒ አይደለም! ” ትላለች ! አዎ ያ ቤት መቃብር
አይደለም … በተስፋ ኑሩ ! አካላችሁ እንጅ አዕምሯችሁን ማሰር የሚቻለው
የለምና ብሩህ ተስፋን ሰንቁ ! ፍትህ ርትዕ የጎደለባችሁን ድምጽ ዛሬም እንደ
ትናንቱ ለምሰለኔዎቻችን አሰማለሁ ! አይዟችሁ !
ለእነ እንቶኔ መረጃ ቅበላየን ጠልታችሁ ላሳደዳችሁኝና ላልተሳካላችሁ ! ” ወደ ገደል አፋፍ ገፋነው ! ” በትምክህት የታበያችሁ ፣
ህልማችሁ ያልተሳካ እኩዮችም ቢሆን ያለመታከት በመስራታችሁ በመንገላታቴ አልተጎዳችሁኝምና ደስ አይበላችሁ ! እግሬና
እጆቸ በካቴና ታስረው ወደማላውቀው የወህኒ ህይወት ስወረወር የማላውቀውን አውቄ ፣ ተምሬና ኑሮ በመከራ እንዴት
እንደሚገፋ እማር ዘንድ ምክንያት ስለሆናችሁኝ አመሰግናችኋለሁ ! አዎ ዛሬ ነጻ ወጥቻለሁ !
ያሳለፍኳቸው 60 የወህኒ ቀናት ራሴን አዙሬ እንዳይ አድርጎኛል። በቀረጣይ ቀናት አረፍ በፍጥነት ከሚስገመገመው የመረጃ
ቅብብሎሽ አውድ ገለል ማለት ባይቻለኝም ለአፍታ አረፍ ማለትን መርጫለሁ! በቀጣይ እረፍት ቀናቶቸ ወደ ብላቴና ልጆቸና
ቤተሰቦቸ ፣ያለፉ እና በውዝፍ የቀሩትን የቀሩ የአረብ ሃገር ስደቱኛ ህይወት ከጋዜጠኝነት ህይዎት ተሞክሮው ጋር አዙሬ
እመለከተው ዘንድ ግድ ይለኛል!
ከአፍታ እረፍት በኋላ እስክንገናኝ ፣ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ: )

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on May 3, 2014
  • By:
  • Last Modified: May 3, 2014 @ 7:30 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar