Read Time:41 Second
በጠራራ ፀሐይ ‹‹አፈቅርሻለሁ!›› በሚል ምክንያት የ17 ዓመቷ ተማሪ ኑሃሚን ጥላሁን በስለት ወግቶ የገደለው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ የሚል ዜና ብንሰማም ለእንደዚህ አይነቱ ነፍሰ ገዳይ የሞት ፍርድ የማይፈርድ የዳኝነት ና የፍትህ ስርአት መኖሩ ግን በጣም ተስፋ አስቋራጭ ነገር ነው ፡፡
አስቡት ምንም ያላጠፋች ህጻን ልጅን የገደለ ነገ ከእስር ተፈቶ በአደባባይ ሲራመድ ማየት በጣም ያሳምማል! !
ሟቿ – የቦሌ ኮሙኒቲ የሕዝብ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪ ነበረች፡፡ ከትምህርት ቤት ስተመለስ፣ ቦርሳዋን እንዳነገተች – እንደወጣች ቀርታለች፡፡
ኑሃሚንን ሕዝብ ተባብሮ ባልቻ ሆስፒታል አድርሷት የነበረ ቢሆንም በሕክምና ጥረት ሕይወቷን ለማትረፍ የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡
በዚህን ጊዜ በሆስፒታል ግቢ የፈሰሰው ሕዝብ በዋይታ – በእንባ ሲራጭ ማምሸታቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡
የወንጀሉ ድርጊት የከተማችን መነጋገሪያ ርዕስ ሆኗል፡፡
እናቷ ወይዘሮ ወይንሸት ወዳጅ ሀዘን በሰበረው ድምፅ፤ ‹‹ … ልጄን ነጠቀኝ! … አበባዬን ነጠቀኝ! … እህቴን፤ ጓደኛዬን ነጠቀኝ! … እህህህ … አቧቷ በአንድ ዓመት ከስድስት ወራት እድሜ ላይ በሞት ተለይቷታል፡፡ ተለይቶናል፡፡ … ብቻዬን፤ ቀረሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፋረደኝ ሲሉ
ገልፀዋል፡፡ ነብስ ይማር !!!




Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Click to email a link to a friend (Opens in new window)
- Click to share on Facebook (Opens in new window)
- Click to share on Twitter (Opens in new window)
- Click to share on LinkedIn (Opens in new window)
- Click to share on Pinterest (Opens in new window)
- Click to share on Tumblr (Opens in new window)
- Click to print (Opens in new window)
Average Rating