www.maledatimes.com በኢትዮጵያ በድጋሚ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ተከሰተ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በኢትዮጵያ በድጋሚ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ተከሰተ

By   /   June 9, 2017  /   Comments Off on በኢትዮጵያ በድጋሚ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ተከሰተ

    Print       Email
0 0
Read Time:56 Second

በኢትዮጵያ ያለው የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ መሔዱ ተጠቆመ፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ መረጃውን ይፋ ያደረገው የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ፣ የግንቦር ወር የዋጋ ግሽበት 8 ነጥብ 7 ሆነ መመዝገቡን ገልጿል፡፡ ይህም ካለፈው ሚያዝያ ወር ጋር ሲተያይ፣ በሸቀጦች ላይ የዋጋ ግሽበት መስተዋሉን ያሳያል ብሏል፡፡ የዋጋ ጭማሪው ከየካቲት ወር ጀምሮ እስከ ግንቦት ወር ድረስ በተከታታይ የተከሰተ ሲሆን፣ በሀገሪቱ የንግድ ስርዓት ላይም ቀውስ መፍጠሩ ተጠቁሟል፡፡

‹‹ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ባልሆኑ ሸቀጦች ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ ለግሽበቱ መጨመር ምክንያት ነው፡፡›› ያለው የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ፣ ‹‹በተለይም ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ እና ማሽላ ዋጋቸው ከፍተኛ ጭማሪ›› ማሳየቱን አስታውቋል፡፡ ጭማሪው በየጊዜው እየተከሰተ መምጣቱ በህዝብ ኑሮ ላይ ጫና ማሳደሩን የሚገልጹት ታዛቢዎች፣ እንዲህ ዓይነት ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በሚታይበት ሁኔታ ውስጥ፣ ደሞዝ ቢጨመር እንኳን ግሽበቱን ለመቋቋም እንደሚያስቸግር ታዛቢዎቹ ይናገራሉ፡፡


በሌላ በኩል ደግሞ ልብስና መጫሚያ፣ የቤት እቃዎች እንዲሁም ማስጌጫዎች ላይም ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ መስተዋሉን ከኤጀንሲው መረጃ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ‹‹ምግብ ነክ ሸቀጦች ግሽበት ካለፈው ሚያዚያ ወር ጋር ሲነፃፀር ከ12 ነጥብ 2 ወደ 12 ነጥብ 3 በመቶ ጨምሯል፡፡›› ሲል በሪፖርቱ ላይ የገለጸው ኤጀንሲው፣ ‹‹ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች ግሽበት ደግሞ ሚያዚያ ወር ላይ ከነበረት 4 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 4 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ብሏል፡፡›› ሲል አስታውቋል፡፡

Source: BBN news June 8, 2017

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 8 years ago on June 9, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 9, 2017 @ 12:24 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar