www.maledatimes.com የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽኑ ከ፳፱ ወደ ፴፩ ክለቦች አድጓል ቀጣይም ሌሎችን ስቴቶች ሊያካልል ይችላል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽኑ ከ፳፱ ወደ ፴፩ ክለቦች አድጓል ቀጣይም ሌሎችን ስቴቶች ሊያካልል ይችላል

By   /   June 15, 2017  /   Comments Off on የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽኑ ከ፳፱ ወደ ፴፩ ክለቦች አድጓል ቀጣይም ሌሎችን ስቴቶች ሊያካልል ይችላል

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 42 Second

ከሰላሳ አራት አመታት በፊት የተጀመርው እና ዛሬ ላይ ኢትዮጵያኖችን አሰባስቦ በየአመቱ በድምቀት የሚከበረው የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ማእከል ከዛሬ አመስት አመታት በፊት ፳፱ ክለቦች የነበሩን ሲሆን – በአሁን ሰአት  ፴፩ ክለቦች በአሁን ሰአት ይዘን እየተጓዝን ሲሆን በሌሎች ስቴቶች ያልተደራጁ ክለቦችን ለማደራጀት እጥራለን በማለት በፌደረሽኑ ስር ያሉ የቦርድ አመራር አካላቶች ገለጹ

በዛሬው እለት ከማለዳ ታይምስ ጋር የስልክ ውይይት ያደረጉት እነዚሁ አባላቶች ቀድሞ በነበሩት የተለያዩ የስራ አካላቶች እና የስራ አባላቶች በተለያዩ ወቅቶች የስፖርት ፌደሬሽኑ ከተለያዩ ማህበረሰቦች እና የፖለቲካ ድርጅቶች የደረሰባቸውን ⶻና የገለጹ ሲሆን ፣ባሳለፉት አምስት አመታትም ከተለያዩ ሰዎች የደረሱባቸው ጫናዎች ፣የፖለቲካ ጽንፈኛ አካል እንደያዙ ተደርጎ እንደተያዘባቸው አስታውሰው የገለጹት እነዚህ አባላቶች ዛሬም ይሁን ትላንት አለበለዚያም ወደፊት እኛ ከህዝብ ጎን እንጂ ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ወግኞች ሆነን ልናገለግል አልተነሳንም ብለው ገልጸዋል።

በፌደሬሽኑ ለሚዘጋጁ ማንኛውም ዝግጅቶች በወቅቱ መጥቶ ለሚጠይቅ ስፖንሰር ቅድሚያ እንሰጣለን፣ ድንኳኖችንም ሆነ ሌሎች ነገሮችን ለመግዛት የሚችል ማንኛውም ድርጅት ከድርጅታችን አገልግሎቶችን ለማግኘት በሩ ክፍት ነው ሲሉ አክለው የገለጹ ሲሆን ፣ ከመረጃ ማእከሎች የመንግስትም ይሁን የግል ወይንም የሲቪክ ማህበራቶች የእኛ ድርጅትን ህልውና የማይነካ ከሆነ እና ነጻ እና ገለልተኛ ሆነው ፣ ያለንን ድክመት እና ጠንካራ ጎን ሪፖርት መስራት ለሚችሉ ወገኖች በሙሉ አሁንም በራችን ክፍት ነው ሲሉ ገልጸዋል ።

በሌላም በኩል ከመንግስትም ጋር ይሁን ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ምንም አይነት ቅርርብነትም ይሁን ግንኙነት ሊኖረን አይችልም ሆኖም ግን እያንዳንዱ ግለሰብ በሚኖረው የራሱ የሆነ የፖለቲካ አመለካከት ፣ከድርጅቱ ጋር አጣምሮ ሊታይ አይገባውም ስለዚህ ከሁሉም ጋር ለመስራት እኛ ዝግጁዎች ነን ሲሉ ጠቁመዋል። ቀድሞ የነበረው የኢትዮጵያ ስፖርት ፌደሬሽን ለሁለት የመከፍል አላማ አልነበረም  በሁለቱ ድርጅት ውስጥ የማዘዝ እና አለመታትዘዝ አላማ ስለነበር እንጂ ለሁለት ተከፍለን አይደለም ፣ በማንኛውም የኢትዮጵያ ችግር ላይ ሰበአዊ መብት ላይ ጥሰት ላይ ሲገልጸው እና ሲታገል የቆየ ነበር ፣ቀድሞም በብዙ የፖለቲካ መንገዶች ሲጠቀስ ቢቆይም እስካሁን ድረስ እንዳይፈርስ አላማውን ይዞ እንዲሄድ ያደረግነው ፣ምናልባትም ወገንተኝነትን ላለማሳየት በመሞከራችን ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

የስፖርት ፌደሬሽኑን አመራር እና ውስጣዊ ደንቦችን በጥልቀት ማየት ምናልባትም ሊረዳ የሚችልበት አጋጣሚ የሚኖረው በምን አይነት አጀንዳ የሚራመድ ድርጅት መሆኑን ለማሳወቅ ሊሆን ይችላል ሲሉ የተናገሩት እነዚሁ ግለሰቦች በቀጣዩ ለሚመጡት በአላቶች በሙሉ ህብረተሰቡ ከቦርድ አመራር አካላቶች ጋር በጋራ በመስራት የህዝብ አገልጋይ መሆኑን እንዲያውቁት ሊረዳ ይችላል ብለው ተናግረዋል

በዘንድሮው የሴያትል ስፖርት ፕሮግራም ላይ ፣አትሌት ሊሊሳ ፈይሳ፣ እና የቀድሞ እግርኳስ ተጨዋች በእንግዳነት እንዲጋበዙ ጥሪ የተደረገላቸው ሲሆን አርቲስት ሻንበል በላይነህ ልዩ የክብር እንግዳ ሆኖ እንደሚቀርብ ተጠቁⶁል ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 8 years ago on June 15, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 15, 2017 @ 1:56 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar