www.maledatimes.com «ለወራት ክስ ሳይመሰረትብኝ፣ ፍ/ቤትም ሳልቀርብ በግፍ ታስሬያለሁ›› ዳኜ፣ ከባ/ዳር እስር ቤት - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

«ለወራት ክስ ሳይመሰረትብኝ፣ ፍ/ቤትም ሳልቀርብ በግፍ ታስሬያለሁ››  ዳኜ፣ ከባ/ዳር እስር ቤት

By   /   August 9, 2017  /   Comments Off on «ለወራት ክስ ሳይመሰረትብኝ፣ ፍ/ቤትም ሳልቀርብ በግፍ ታስሬያለሁ››  ዳኜ፣ ከባ/ዳር እስር ቤት

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 12 Second

ስም፡- ማሩ ዳኜ

ዕድሜ፡- 36

አድራሻ፡- ባህር ዳር ከተማ

አሁን በእስር የምገኝበት ቦታ፡- ‹በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረሚያ ቤት መምሪያ

ለእስር የተዳረግሁበት ምክንያት፡- ነሐሴ 01/2008 ዓ.ም በዚሁ በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር ተደርጎ የነበረውን የተቃውሞ ህዝባዊ ሰልፍ ጠርተሃል፣ አስተባብረሃል በሚል ነው፡፡

በይፋ የተመሰረተብኝ የክስ አይነት፡- ለእስር ከተዳረግሁበት ነሐሴ 2008 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በይፋ ክስ አልተመሰረተብኝም፡፡ ሆኖም ግን የክልሉ ፍትህ ቢሮ እኔንና አብረውኝ የታሰሩትን ሰዎች ለ11 ሰዎች ህይወት መጥፋት፣ ለ59 ሰዎች አካል ጉዳት እና ለ29 ሚሊዮን ብር ውድመት ተጠያቂነት ስለሚጠረጠሩ በሚል ዋስትናችን እንዲነፈግ ለክልል ጠ/ፍርድ ቤት በጽሁፍ አቤቱታ ቀርቦ በእስር ላይ መገኘቴን አውቃለሁ፡፡

በእስር በምገኝበት ወቅት የሚከተሉት የመብት ጥሰቶች ተፈጽመውብኛል፡

  1. ያለምንም ይፋዊ ክስ ለረጂም ወራት ታስሬያለሁ፡፡
  2. በመደበኛነት ፍርድ ቤት መቅረብ አልቻልሁም፡፡ ይህም ያለኝን አቤቱታ የማሰማት እድል ነፍጎኛል፡፡
  3. ለእስር ስዳረግ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ታፍኜ ነው የታሰርሁት፡፡
  4. ስድብና ዛቻ ደርሶብኛል፡፡
  5. የታሰርሁት ካስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅ በፊት ቢሆንም በአዋጁ ሰበብ ጠበቃ እንኳ እንዳላገኝ ተደርጌ ታስሬያለሁ፡፡
  6. ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ክፍል ውስጥ በአንድ አልጋ ላይ አራት ሰዎች ጋር እንድተኛ ተገድጃለሁ፡፡

የኋላ ታሪክ:

በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ በህጋዊነት ተመዝግበው የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በሚያደርጉ ሦስት ፓርቲዎች (ቅንጅት፣ አንድነት እና ሰማያዊ) ውስጥ አባል በመሆን የፖለቲካ አራማጅ ሆኜ ስሳተፍ ቆይቻለሁ፡፡ ፖለቲካ ውስጥ ገብቼ ስለሰው ልጆች መብት መከበር በመናገሬ፣ በመታገሌ ከደስታ ውጭ የሚሰማኝ ነገር የለም፡፡ በዚህ ድርጊቴ ለአፍታ እንኳ እስር ቤት መግባት አልነበረብኝም፡፡

የሦስት ልጆች አባት ነኝ፡፡ እስከታሰርሁ ድረስ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ እየሰራሁ፣ በዚያውም ራሴን ለማሻሻል በዚሁ ተቋም እየተማርሁ ነበር

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 8 years ago on August 9, 2017
  • By:
  • Last Modified: August 9, 2017 @ 8:00 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar