- የመንግስት አካላት በህብረተሰቡ ላይ ምንም አይነት የሰበአዊ መብት ከለላ ለማድረግ አለመብቃታቸው ፣በአስተዳደሩ ላይ የእውቀት ማነስ እንዳለም ተጠቁⶁል።

በቤኒሻንጉል ጉምዝና በደቡብ ክልሎች ጥቃት የተፈጸሙት መንግሥትና የፀጥታ አካላት መከላከል ባለመቻላቸው መሆኑ ተገለጸ
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞንና በደቡብ ክልል ካፋና ሸካ ዞኖች በተከሰቱ ግጭቶች፣ መንግሥትና የፀጥታ አካላት አስቀድመው በአግባቡ መከላከል ባለመቻላቸው ጥፋቶች እየተከሰቱ መሆኑን አስታወቁ፡፡ ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር (ዶ/ር) በሐዋሳ ከኢሕአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ ነው፡፡
ኮሚሽነሩ በእነዚህ አካባቢዎች ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የሰብዓዊ መብቶች እየተጣሱ መሆኑን ገልጸው፣ ዜጎች ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስና ሀብት የማፍራት መብታቸው አደጋ ላይ መውደቁን አስታውቀዋል፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪዎች ከማረፊያቸው መውጣት ባለመቻላቸው ሳቢያ፣ የምርመራ ሥራቸውን ማከናወን እንዳልቻሉና እስካሁን ያለውን የጉዳት መጠን ማወቅ አለመቻሉን አስታውቀዋል፡፡
‹‹መርማሪዎቻችን ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ አልቻሉም፡፡ ይህም ግጭቱና ሁከቱ የከፋ መሆኑን ያሳያል፤›› ያሉት ኮሚሽነሩ፣ መርማሪዎቹ ሁኔታዎች የሚሻሻሉ ከሆነ ከነገ ጀምረው ሥራቸውን እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል፡፡ መንግሥት የፀጥታ ማረጋጋት ሥራ እያከናወነ ቢሆንም፣ በሁሉም አካባቢዎች እየተከናወነ እንዳልሆነም ተናግረዋል፡፡
Average Rating