www.maledatimes.com ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን አከሰመ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን አከሰመ

By   /   January 5, 2019  /   Comments Off on ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን አከሰመ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 8 Second

እሑድ ታኅሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. የሰባተኛ ዓመት ምሥረታ በዓሉንና  ጠቅላላ ጉባዔውን ያከናወነው ሰማያዊ ፓርቲ ዜግነት ላይ አትኩሮት በማድረግ ለሚቋቋመው ፓርቲ ምሥረታ ይረዳ ዘንድ ራሱን በማክሰም፣ እንደ አዲስ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ውህደት ለመፍጠር መወሰኑን አስታወቀ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ መክሰምን ውሳኔ አስመልክቶ ሰኞ ታኅሳስ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. መግለጫ የሰጡት አመራሮቹ፣ አንድ ትልቅ አገራዊ ፓርቲ መፍጠር በማስፈለጉ ምክንያት መክሰሙን ይፋ አድርገዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ላለፉት ሦስት ወራት ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ለዴሞክራሲና አንድነት ንቅናቄ፣ ከኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) እንዲሁም አቶ አንዱዓለም አራጌና አቶ ግርማ ሰይፉን ከመሳሰሉ የቀድሞ አንድነት ፓርቲ አባላት ጋር ውህደት ለመፍጠር ሲያደርጉት የነበረው ውይይት ተጠናቆ፣ ፓርቲዎች ማንነታቸውን በማክሰም በዜግነትና በማኅበራዊ ፍትሕ ላይ መሠረት ያደረገ ፓርቲ ለመመሥረት መወሰናቸው የሚታወስ ነው፡፡

ይህንን ስምምነት ተከትሎ ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን በማክሰም አርዓያነት ማሳየት በመፈለጉ ውሳኔው መተላለፉን፣ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታነህ ባልቻ ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላላ ጉባዔው ፓርቲውን አፍርሶ አዲሱን ፓርቲ ለመመሥረት ሥራ ለመጀመር ወስኗል ሲሉ አቶ ጌታነህ አክለው ገልጸዋል፡፡

አዲስ የሚቋቋመው ፓርቲ ከመጋቢት 30 ቀን 2011 ዓ.ም. በፊት ምሥረታውን በይፋ እንደሚያስታውቅ የገለጹት አቶ ጌታነህ፣ አሁን ያለው የብሔር ፖለቲካ እንደማያሠጋና የዜግነት ፖለቲካን በቀላሉ ሕዝቡ ውስጥ ማስረፅ ይቻላል ተብሎ እንደሚታመን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ጋር በጋራ ለመሥራት ሰማያዊ ፓርቲ ንግግር ጀምሮ እንደነበር በማስታወስ አሁን የሁለቱ ፓርቲዎች በጋራ የመሥራት ጉዳይ ከምን ደረሰ በማለት ሪፖርተር ላቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ጌታነህ ሲመልሱ፣ ‹‹እነሱ እንደ እኛ ቁርጠኛ መሆን አልቻሉም፡፡ እኛ አሁንም ቢሆን ፓርቲያችሁን አፍርሳችሁ ኑ ብለናል፡፡ ነገር ግን ፓርቲ ለማፍረስ ወገቤን አሉ፤›› ብለዋል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 6 years ago on January 5, 2019
  • By:
  • Last Modified: January 5, 2019 @ 11:21 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar