www.maledatimes.com ፕሬዚዳንት ትራምፕ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ ይችላሉ። አድማስ ሬዲዮ እንደዘገበው - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ ይችላሉ። አድማስ ሬዲዮ እንደዘገበው

By   /   January 8, 2019  /   Comments Off on ፕሬዚዳንት ትራምፕ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ ይችላሉ። አድማስ ሬዲዮ እንደዘገበው

    Print       Email
0 0
Read Time:53 Second

ማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል

የአሜሪካ መንግስት መሪዎቹ ባለመስማማታቸው ምክንያት በከፊል ከተዘጋ አንድ ወር ሊሆነው ነው። በወቅቱ መዘጋቱ የሚያመጣው የጎላ ችግር እንደማይኖር ሲገለጽ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ቀኑ በተራዘመ ቁጥር፣ በከፊል የመዘጋቱ እና ከ400ሺ ያላነሱ የፌዴራል መንግስት ሰራተኞች ከሥራና ከደሞዝ ውጭ መሆናቸው የጎላ ችግር እያመጣ ይገኛል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፣ ከድንበር አጥር መስሪያ 5 ቢሊዮን ዶላር ካልተሰጠኝ፣ ይለቀቅ በተባለው በጀት አልስማማም በማለታቸው፣ ዲሞክራቶችም ፕሬዚዳንቱ የጠየቁትን ገንዘብ በበጀት ውስጥ አናካትትም በማለታቸው ውጥረቱ አይሎ ይገኛል።

ይህን አስመልክቶ ዛሬ ማምሻውን ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለአሜሪካ ህዝብ የቀጥታ የቴሌቪዥን ንግግር እንደሚያደርጉ ታውቋል። ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው የሚያተኩሩት፣ 5 ቢሊዮን ዶላር ለድንበርና ተያያዥ ጉዳዮች የጠየቁት እንዲሁ እንዳልሆነና በደቡቡ የሜክሲኮ – አሜሪካ ድንበር አካባቢ ያለውን የስደተኞች ፍልሰት ስጋት ለማብራራት እንደሆነ ተገምቷል።

Image may contain: one or more people, suit, outdoor and closeup

ፕሬዚዳንቱ በማታው ንግግራቸው “አገራቸው ትልቅ የስደተኞች ወረራ እንዳጋጠማትና፣ የደቡቡን ድንበሯን በሚገባ ማጠር፣ የኢሚግሬሽን ዳኞችን ማብዛት፣ የማሰሪያ ቦታዎችን መጨመር፣ የ ዕጽ ማስተላለፊያ መንገደችን ማብዛትና መቆጣጠሪያውን ዘመናዊ ማድረግ” በመግለጽ “የጠየኩት 5 ቢሊዮን ዶላር ለዚህ ነውና የአሜሪካ ህዝብ ፍረደኝ” እንደሚሉ ይገመታል።

አያይዘውም “ይህ የማይሆን ከሆነና፣ ዲሞክራቶች ገንዘቡን በጀትን ውስጥ አልለቅም ካሉ፣ ከሌላ የመከላከያ የተለቀቀ በጀት ላይ በመቀነስ የድንበር ግንቡን ለመስራት እንደሚገደዱ” በመግለጽ ለዚህም ደግሞ አስቸኳይ ጊዜ ማወጅ አስፈላጊነቱን ይገልጻሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 6 years ago on January 8, 2019
  • By:
  • Last Modified: January 8, 2019 @ 5:17 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

Skip to toolbar