![Image may contain: 1 person, beard](https://scontent-atl3-1.xx.fbcdn.net/v/t1.0-9/71745864_3096270080445177_5848200596070334464_n.jpg?_nc_cat=102&_nc_eui2=AeFcM1lRIGEg0j54wL3qRUSy4YNhoVWloaD-MJvdvqMPYMaBV2FRtZJWuTSBFJK0uPKrVs8eC0OTAWQ9uXD4ah_XHUBcLPu7bacawa0fjmaYmA&_nc_oc=AQlC7wU-peksfE9ExUhoRaRV6fTnEOwoyFt6RO3iq3ioKn4beENe6jxr3UgLyDJJ70Y&_nc_ht=scontent-atl3-1.xx&oh=c11925ea0cd21218d842204f79f7e8a0&oe=5E2A5AA0)
” ስለሽመልስ አብዲሳ በሰጠሁት አስተያየት አሳስተህናል ለምትሉ ወገኖቼ ትልቅ ይቅርታ “
የተወሰንን ግለሰቦች ኦሮአማራ እያልን ስንጮህ ሕውሃት እና የኦነግ አጋሮች ሲሰድቡን ከረሙ፡፡ የእነርሱ መንጫጫት እንብዛም አሳስቦን አያውቅም ነበረ፡፡
አሁን ደግሞ በሚያስደነግጥ እና በሚያሳፍር ትችት እና ዲስኮርስ የአማራን እና የኦሮሞን ግንኙነት ለማክሰም ሞከርክ፡፡ ሆኖም ግን ለብዙ ዘመናት በአብሮነት የኖሩት ህዝቦች፤ በፓርቲና በግለሰቦች ፈቃድ ቀድሞውንም ያልተመሰረተ በመሆኑ ሊፈርስ አይችልም፡፡
እንደዚህ አይነት ሕውሃታዊ፤ኦነጋዊ እና አክራራዊ ገለፃ አንተ ይዘህ በመቅረብህ እኔ ብቻ ሳልሆን፤ ስትሾም “እንኳን ደስ ያለህ” ብለው መልዕክት የላኩልህ የፍልስፍና አሰተማሪዎችህም በእጅጉ አዝነውብሃል፡፡
አማራ ተባለ ነፍጠኛ በታሪኩ ለማንም ተንበርክኮ አያውቅም፤ ይህንን እውነታ እንኳንስ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ያለ ሕዝብ ይቅርና፤ ቱርኮችም፣ ግብፃችም፣እንዲሁም ጣሊያኖችም ጠንቅቀው ያውቀሉ፡፡
ልጅ ሽመልስ እንደአስተማሪህ ያለኝ ምክር፡- በንግግርህ ላስቀየምከው ህዝብ ትልቅ ይቅርታ በይፋ ወጥተህ መጠየቅ ይኖርብሀል፡፡ በተጨማሪም ራስህን ሁን፣ ለሙገሳ እና የግለሰቦችን ቅቡልነት ለማግኘት ስትል ሌላውን ሰው ለመሆን አትሞክር፤ በተቻለህም መጠን የአክራራዊነት መንፈስ ከራስህ ላይ አርቅ፤ መጠቀሚያም አትሁን፡፡
በመጨረሻም፤
ስለሽመልስ አብዲሳ በሰጠሁት አስተያየት አሳስተህናል ለምትሉ ውገኖቼ ትልቅ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ለነገሩ የተከሉት ዛፍ ቀጥ ብሎ ይወጣል ሲሉ ከፍ ሲል ሊጎብጥ ይችላል እና እንዲሉ፡፡
ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Click to email a link to a friend (Opens in new window)
- Click to share on Facebook (Opens in new window)
- Click to share on Twitter (Opens in new window)
- Click to share on LinkedIn (Opens in new window)
- Click to share on Pinterest (Opens in new window)
- Click to share on Tumblr (Opens in new window)
- Click to print (Opens in new window)
Average Rating