የኢትዮ ቴሌኮም የቀድሞ ዳይሬክተር የተጠረጠሩበት የ44.5 ሚሊዮን ዶላር ግዥ ውድቅ ተደረገ
የዓለም ገነት ቆርቆሮ ባለቤት የክስ መመሥረቻ ጊዜ ተራዘመ በሶማሌ ክልልና በባሌ ዞን የሞባይልና ሲዲኤምኤ (የቴሌ ታወር ሥራዎች) ግንባታን በጥቅም ተመሳጥረው ያለ ጨረታ ለሜቴክ ሰጥተዋል ተብለው በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የኢትዮ ቴሌኮም የኤንጂፒኦ የቀድሞ ዳይሬክተር፣ ከዩኒቨርሲቲዎች ኔትወርክ ግንባታ ጋር በተያያዘ ቀርቦባቸው የነበረው የ44.5 ሚሊዮን ዶላር ግዥ ውድቅ ተደረገ፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ተጠርጣሪው […]
Read More →ሕወሓት ሰሞኑን የተሰበሰበው መደበኛ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ለማድረግ እንደሆነ ተገለጸ
የህወሃት ድክመት እምኑ ላይ እንደሆነ ማወቅ ተስኖታል!! አቶ ጌታቸው አሰፋን የተመለከተ አጀንዳ አልነበረም የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ሰሞኑን የተሰበሰበው መደበኛውን የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ለማድረግ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት የክልሉ መንግሥት ካለፈውሐምሌ ወር 2010 ዓ.ም. ወዲህ ባሉት ጊዜያት ያከናወናቸውን ሥራዎች እንዲሁም ፀጥታና ደኅንነትን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ግምገማ ማድረጉን የድርጅቱሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ለሪፖርተር ገለጹ። ሕወሓት ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ስብሰባ ባለፈው ዓርብ አጠናቋል። ይህ ስብሰባ የተለየ አለመሆኑን የተናገሩት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ በፓርቲ ደረጃ በመገናኘትየክልሉን መንግሥት የሥራ አፈጻጸምና ወቅታዊ ሁኔታዎች ከተገመገሙ ቆየት በማለቱ የተጠራ ስብሰባ ቢሆንም የተለመደ የፓርቲ ሥነ ሥርዓት መሆኑንምአመልክተዋል። በዚህ ስብሰባ የክልሉ መንግሥት ባለፉት ወራት ያከናወናቸው የልማትና የማኅበራዊ ጉዳዮች ሲገመገሙ፣ በተጨማሪም በወቅታዊ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮችላይ ውይይት መካሄዱን ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የሕወሓት ዋነኛ መወያያ አጀንዳ ባይሆንም ከወራት በፊት የተከፈተው የኢትዮ ኤርትራ ድንበር በቅርቡ የተዘጋበት ምክንያትምን እንደሆነ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንትና የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ማብራሪያ እንዲሰጡበት ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። ጉዳዩ በቀጥታ የፌዴራል መንግሥትን የሚመለከት ቢሆንም፣ ጉዳዩን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲከታተሉት ማዕከላዊ ኮሚቴው መስማማቱን ገልጸዋል። በክልሉ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች እንዲሁም በአገር ደረጃ የሚስተዋለው የፀጥታ ችግርን በተመለከተ ውይይት መደረጉን የገለጹት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ምንምእንኳን ሕወሓት በአገር አቀፍ ደረጃ ያለው ሚና ትንሽ ቢሆንም ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመተባበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ መወሰኑን ተናግረዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በዚህ ሳምንት ለፓርላማ ባቀረበው ሪፖርት በከባድ የሰብዓዊ መብት ወንጀል የተጠረጠሩት የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ በቁጥጥር ሥር ለማዋል ለትግራይ ክልል ጥያቄ ቢቀርብም ክልሉ ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆኑና የክልሉ አመራር አቶጌታቸውንም ሆነ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ሸሽጓል በማለት ዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ ተናግረው ነበር። የሕወሓት ስብሰባ ከዚህ ወቀሳ በኋላ የተካሄደ በመሆኑ የአቶ ጌታቸው ጉዳይ የውይይቱ አካል ይሆናል የሚል ግምት በበርካቶች ዘንድ ነበር። የአቶ ጌታቸው አሰፋን ጉዳይ የተመለከተ ውይይት ተካሄዶ እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ውይይት አለመደረጉንና ፓርቲው በጉዳዩላይ ሊወያይም እንደማይችል ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው አሰፋ የሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ አባል መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በዚህ የሕወሓት ስብሰባ ላይ አለመገኘታቸውን ሪፖርተር ከአቶ ጌታቸው ረዳለማረጋገጥ ችሏል። በኢሕአዴግ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ በየሦስት ወሩ፣ ማዕከላዊ ኮሚቴው ደግሞ በየስድስት ወሩ መገናኘት እንዳለበት ቢደነግግም፣ አስቸኳይ ሁኔታዎች ሲኖሩ ሊጠራ እንደሚችል ይደነግጋል። ይሁን እንጂ ሥራ አስፈጻሚው ከተሰበሰበ ቆይቷል። ይህ ጉዳይ በሕወሓት የሰሞኑ ስብሰባ ተነስቶ እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው፣ ‹‹አልተነሳም። ሕወሓትበዚህ ጉዳይ ለምን ይወያያል? ስብሰባውን መጥራት ያለበት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ነው፤›› ብለዋል። ነገር ግን የአገሪቱ ወቅታዊ የፀጥታና የደኅንነት ጉዳዮች በኢሕአዴግ ደረጃ ውይይት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የተናገሩት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ‹‹ኢሕአዴግበቅርቡ ስብሰባ ካልጠራ በእኛ በኩል ስብሰባ እንዲጠራ ጥያቄ ልናቀርብ እንችላለን፤›› ብለዋል። በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሕወሓት ሊቀመንበር ከኃላፊነት ለመልቀቅ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር የሚወራውንም አስተባብለዋል።
Read More →የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ያልተለመዱ አሠራሮች ተግባራዊ ይደረጋሉ አሉ
የአዲስ አበባ ከተማን ቁልፍ ከተረከቡ በኋላ ሪፖርታቸውን ለመጀመርያ ጊዜ ለምክር ቤት ያቀረቡት ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር)፣ በከተማው በ27 ዓመታት ያልተለመዱ አሠራሮች ተግባራዊ መሆናቸውንና ወደፊትም እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ምክትል ከንቲባው በተለይ በመታወቂያ አሰጣጥ፣ በመኖሪያ ቤት አቅርቦት፣ በመልሶ ማልማት ፕሮግራሞች፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በውኃ አቅርቦት፣ በወጣቶችና በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች አስተዳደሩ የሚከተለውንና እየተከተለ ያለውን አዳዲስ አሠራሮች በጥልቀት አብርተዋል፡፡ ምክትል […]
Read More →በሃሰተኛ ክስ ልጃቸውን ገድለዋል ተብለው እድሜ ልክ የታሰሩት ታራሚ ህይወታቸው አለፈ በዘለአለም ገብሬ እንደታ
ለእረጅም ዘመናት የህይወት ጊዜአቸውን በእስር ያደረጉት እና ያለምንም ጥፋታቸው በፍትህአብሔር ክስ የተመሰረተባቸው የሰማኒያ አመቱ አዛውንት ከእረጅም የእስርቤት ስቃይ እና መከራ በኋላ በዛሬው እለት ህይወታቸው ማለፉን ከማረሚያ ቤት የደረሰን መረጃ ያመለክታል። እንደ መረጃ ዘገባው ከሆነ አዛውንቱ ምንም በማያውቁት እና በአልተረዱት ሁኔታ ልጃቸው በድንገት ሲያልፍ እርሳቸው ቀጥቅጠው እንደገደሉት አድርገው ፖሊሶች የክስ መዝገብ በማቅረባቸው ምክንያት ወንጀሉ በከፍተኛ ፍርድ […]
Read More →ፍርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ ሆነው መሥራት አለመቻላቸውን ፕሬዚዳንቷ ተናገሩ
በሶማሌ ክልል የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ሰብሳቢ የክልሉ ፕሬዚዳንት ነበሩ የፌዴራልም ሆኑ የክልል ዳኞች የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሕገ መንግሥቱ ከፍተኛ ኃላፊነት የተጣለባቸው ቢሆንም፣ የዳኝነት ነፃነታቸው በአስፈጻሚውና በሌሎች አካላት ጣልቃ ገብነት ምክንያት በመገደቡ ገለልተኛ እንዳልነበሩ፣ ዜጎችም በዳኝነት አካሉ ላይ አመኔታ እንዳይኖራቸው ማድረጉን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተናገሩ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት ሥራ አስተዳደር የሚያጋጥሙ ውስጣዊና […]
Read More →ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን አከሰመ
እሑድ ታኅሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. የሰባተኛ ዓመት ምሥረታ በዓሉንና ጠቅላላ ጉባዔውን ያከናወነው ሰማያዊ ፓርቲ ዜግነት ላይ አትኩሮት በማድረግ ለሚቋቋመው ፓርቲ ምሥረታ ይረዳ ዘንድ ራሱን በማክሰም፣ እንደ አዲስ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ውህደት ለመፍጠር መወሰኑን አስታወቀ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ መክሰምን ውሳኔ አስመልክቶ ሰኞ ታኅሳስ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. መግለጫ የሰጡት አመራሮቹ፣ አንድ ትልቅ አገራዊ ፓርቲ መፍጠር በማስፈለጉ […]
Read More →ሰላም ለማስፈን ከፖለቲካ ድርጅቶች ይልቅ ሕዝቡ እንዲሳተፍ ተጠየቀ
በአገሪቱ ሰላምን ለማስፈን በሚካሄደው እንቅስቃሴ ውስጥ ከፖለቲካ ድርጅቶች ይልቅ ሕዝቡን ማሳተፍ እንደሚያስፈልግ፣ ሕዝቡን ያላሳተፈ እንቅስቃሴም ወደ ውድቀት ሊያመራ እንደሚችል የአማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (አህኢድ) አስታወቀ፡፡ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) እና የአማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (አህኢድ) በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ሰኞ ታኅሳስ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. መፈረማቸውን አስመልክተው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል […]
Read More →የሃይማኖት መሪዎችና የአገር ሽማግሌዎች የአገሪቱ ሰላም ከምንጊዜውም በላይ አስጨንቆናል አሉ
በኢትየጵያውያን ወንድማማቾች መካከል አለመከባበርና አለመተማመን የሚፈጥሩ ተጨባጭ ችግሮች እየታዩ ከመሆናቸውም ባለፈ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የእርስ በርስ ዕልቂት የሚያስከትሉ ግልጽ የወጡ ግጭቶች እየታዩ መሆኑንና ሁኔታው ከምንጊዜውም በላይ በአሁኑ ወቅት እያስጨነቃቸው እንደሆነ የሃይማኖት መሪዎችና የአገር ሽማግሌዎች ተናገሩ፡፡ የሃይማኖት መሪዎችና የአገር ሽማግሌዎች በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በተለይም በምዕራብና በምሥራቅ ኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሶማሌ፣ በአፋር፣ በትግራይና በአማራ ክልሎች […]
Read More →የ48 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሳይጀመር ግማሽ ዓመት ተጠናቀቀ
በተያዘው የበጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ 48 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እንደሚጀመር ቢታቀድም፣ ግንባታው ሳይጀመር የበጀት ዓመቱ የመጀመርያው ስድስት ወራት ተጠናቀቁ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶቹን ግንባታ ለማካሄድ አቅዶ የነበረው በቦሌ ክፍለ ከተማ፣ በቦሌ አራብሳ፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፣ በኮዬ ፊጬ አካባቢዎች በሚገኙ ስምንት ሳይቶች ነበር፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና […]
Read More →የትምባሆ የአልኮልና የመድኃኒት ቁጥጥር አዋጅ የበለጠ ጥብቅ እንዲሆን ጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ጠየቁ
የትምባሆ፣ የአልኮል፣ የመድኃኒትና ምግብ ነክ ምርቶችን ለመቆጣጠር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ የበለጠ ጥብቅ እንዲሆን የጤናጥበቃ ሚኒስትሩ ምክር ቤቱን ጠየቁ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕፃናት ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ረቂቅ አዋጁን በዝርዝር ለመመርመር ዛሬ ረቡዕ ታኅሳስ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄደው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን በረቂቅ አዋጁ ላይ የተቀመጡ ክልከላዎች በቂ አለመሆናቸውንበመገንዘብ ክልከላዎቹ የበለጠ ጥብቅ እንዲሆኑ የማሻሻያ ሐሳብ ለቋሚ ኮሚቴው አቀረቡ። ካቀረቧቸው ጥብቅ የማሻሻያ ክልከላዎች መካከል እንደ ቢራ ያሉ የአልኮል ምርቶች በኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች ማለትም በሬዲዮና በቴሌቪዥን ከምሽቱ 3፡00ሰዓት እስከ ሌሊት 12፡00 ሰዓት ብቻ እንዲተዋወቁ በረቂቁ ላይ የተቀመጠው ድንጋጌ ተሻሽሎ፣ የአልኮል ምርቶች በተጠቀሱት ሚዲያዎች ሙሉ ለሙሉእንዳይተዋወቁ ክልከላ እንዲጣል የሚል የማሻሻያ ሐሳብ አቅርበዋል። የአልኮል ምርቶች ማለት የአልኮል ይዘታቸው ከሁለት በመቶ በላይ መሆኑን የሚገልጸው የረቂቅ አዋጁ ትርጓሜ ተሻሽሎ የአልኮል ይዘቱ ከ0.5 በመቶ በላይበሚል እንዲሻሻልም የጠየቁ ሲሆን፣ ለዚህ ያቀረቡት ምክንያትም አልኮል የሚያመርቱ ኩባንያዎች ከሁለት በመቶ በታች የሆኑ የአልኮል ምርት ዓይነቶችንበማምረት የአልኮል መጠጦች በተጠቀሱት ሚዲያዎች እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ነው። የአልኮል መጠጦችን ለማስተዋወቅና ገበያውን ለማስፋት ከፍተኛ ሽልማቶችን የሚያስገኙ ዕጣዎችን በቆርኪ ላይ ማያያዝ ክልከላ እንዲደረግበትም ሐሳብአቅርበዋል። ሚኒስትሩ እነዚህ ጥብቅ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ቋሚ ኮሚቴውን በጽሑፍ መጠየቃቸውን ተናግረዋል። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት በሕዝባዊ ውይይትመድረኩ ላይ የተገኙ የጤና ባለሙያዎች፣ ታዋቂ አርቲስቶች፣ ወጣት ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች ረቂቅ አዋጁ የበለጠ ጥብቅ እንዲሆንና የአልኮልማስታወቂያ እንዲቆም በተደጋጋሚ በመጠየቃቸው ነው። የትምባሆና አልኮል ሽያጭን በተመለከተ ረቂቅ ሕጉ ላይ ሁለቱም ምርቶች ከ18 ዓመት ዕድሜ በታች እንዳይሸጡ የሚደነግገው አንቀጽ ተሻሽሎ ከ21 ዓመትበታች እንዲባል ጠይቀዋል። ይኼን ሐሳብም በሕዝባዊ የውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት አብዛኞቹ ደግፈውታል። የኢትዮጵያ ትምባሆ ኢንተርፕራይዝ የሥራ ኃላፊዎች በውይይት መድረኩ ላይ ተገኝተው ረቂቅ የቁጥጥር ሕጉ በኩባንያው ላይ ሊያደርስ ይችላል ያሏቸውንሥጋቶች አንስተዋል። ካነሷቸውም ሥጋቶች መካከል ዋነኛው በረቂቁ የተቀመጡ የቁጥጥር ሕጎች የኮንትሮባንድ የሲጋራ ንግድን ያበረታታል የሚል ነው። ይኼም ከሥጋት ባለፈተጨባጭ መሆኑን ለማስረዳት በአሁኑ ወቅት እንኳን የአገሪቱ የሲጋራ ገበያ 44 በመቶው በኮንትሮባንድ በሚመጡ ምርቶች የተያዘ መሆኑን አንስተዋል። የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት ምላሽ አጠቃላይ የኮንትሮባንድ ንግድን በተመለከተ መንግሥት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንጠቅሰው፣ የሲጋራ ኮንትሮባንድ ንግድን በተመለከተ ግን የትምባሆ አምራች ኩባንያዎች ጥብቅ የቁጥጥር ሕግ መንግሥታት እንዳያወጡባቸው ሲሉ ራሳቸውየኮንትሮባንድ የሲጋራ ንግድ እንዲስፋፋ በማድረግ አልያም መስፋፋቱን በመደገፍ መንግሥት የቁጥጥር ሕግ ቢያወጣ ኮንትሮባንድ እንዲስፋፋ ከማድረግየዘለለ ትርጉም እንደማይኖረው ለማስመሰል እንደሚሞክሩ ለመድረኩ አስረድተዋል። ከመድኃኒት አስመጪዎችም በርከት ያሉ ሥጋቶች የተነሱ ሲሆን፣ ቋሚ ኮሚቴው የተነሱትን በግብዓትነት ወስዶ ተጨማሪ የውይይት መድረክ መጥራት አስፈላጊመሆኑን ካመነበት የሚከለክለው ነገር ባለመኖሩ ሊጠራ እንደሚችል ገልጿል። ይሁን እንጂ ረቂቅ አዋጁ የንግድ ጥቅማቸውን የሚነካባቸውም ሆኑ ሌሎች ለቋሚ ኮሚቴው አመራሮችና አባሎች በግል ስልካቸው ላይ በመደወል ማስቸገርእንደሌለባቸውና ተግባሩ እንዲቆም አሳስበዋል።
Read More →